ወቅታዊው የገንዘብ ድጋፍ ምዕራፍ
ወቅታዊው የገንዘብ ድጋፍ ምዕራፍ (እ.ኤ.አ. ከ ጃንዋሪ 1. 2025 - ዲሴምበር 31 2026)፡
የፕሮጀክት ምዕራፍ 3 አላማ የፈጠራ እና የመማሪያ የመረጃ መድረክን "hub4africa" የበለጠ ማዳበር እና ማስፋፋት ነው። አዳዲስ ቡድኖችን እና ተግባሮችን ለማዋሃድ በአሁን ሰዓት ያለውን የመሳሪያ ደንብ ተግባራዊነቱን ማስፋፋት ነው።
የኮርሶችን ብዛት በማስፋፋት ይዘቱን በተለይ ከክልላዊ እና ከስራ ገበያ መስፈርቶች ጋር ማጣጣም ሆኗል። የመድረኩ ተደራሽነቱ ከአውታረ መረብ አጋሮች፣ የሰለጠኑ አሰልጣኞች እና ከማህበራዊ ሚዲያ ጋር የቅርብ ትብብር በማድረግ በቋሚነት ያለማቋረጥ ይጨምራል።
ዋናው የዚህ ምዕራፍ አዲስ አካል በጀርመን ውስጥ እውቅና የተሰጣችው የከፊል ብቃቶች (TQs) ውህደት ነው።
እነዚህ ችሎታ ያላቸው ሠራተኞች በሙያ ማሰልጠኛ ሕግ (BBiG) መሠረት ወደ ሙሉ የሙያ ብቃት የሚያመሩ እና ከሙያው ጋር የተያያዙ ብቃቶችን ቀስ በቀስ እንዲያገኙ ያስችላቸዋል። እነዚህ ብቃቶች የከፊል የብቃት ሞጁሎች የንድፈ ሃሳብ ይዘትን፣ የተግባር መመሪያን እና የድርጅት ውስጥ የብቃት ስልጠናን ምዕራፎችን ያካትታሉ። ሰልጠናው በተሳካ ሁኔታ ሲጠናቀቅ ተሳታፊዎቹ በጀርመን ውስጥ እውቅና ያለው የምስክር ወረቀት ይቀበላሉ.
የሞጁሎቹ ትምህርት የሚሰጠው አና ፈተና የሚደራገው በጀርመንኛ ቋንቋ ነው, ይህም ቴክኒካዊ ብቻ ሳይሆን ከሥራ ጋር የተገናኘ የቋንቋ ችሎታችን ያረጋግጣል.
"hub4africa" በዚህ አዲስ አቀራረቡ በጥሩ ቁጥጥር የሚደረግበት የሰለጠኑ ባለሙያዎችን ወደ ጀርመን እንዲገቡ ይደግፋል ፣ በተለይ በባየርን ያለውን የሰለጠኑ ባለሙያዎች እጥረትን ለመቅረፍ ትልቅ አስተዋፅኦ ያደርጋል። መድረኩ በጀርመን ውስጥ ትምህርትን፣የሙያ ስልጠናን እና ስደትን በፈጠራ መመዘኛ መንገድ አጣምሮ በልዩ መልክ ያቅርባል ።